የአፍሪካ አገራት አሁን ላይ ከብሪክስ ከፍተኛ ጥቅም እያገኙ ነው - ደቡብ አፍሪካዊ ተንታኝ
09:01 17.05.2026 (የተሻሻለ: 09:04 17.05.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የአፍሪካ አገራት አሁን ላይ ከብሪክስ ከፍተኛ ጥቅም እያገኙ ነው - ደቡብ አፍሪካዊ ተንታኝ
በደርባን የቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የብሪክስ ምርምር ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ፉሉፌሎ ኔትስዌራ፤ ብሪክስ በተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት፣ በዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት እና በዓለም ባንክ ላይ ለረጅም ጊዜ የዘገዩ ለውጦችን ለማምጣት እንደ ትልቅ አበረታች ኃይል ያገለግላል ሲሉ ገልፀዋል።
በርካታ የደቡባዊ ዓለም አገራት ለዓመታት እንዲህ ዓይነት ማሻሻያዎች እንዲደረጉ ቢወተውቱም ምንም ዓይነት ውጤት አላገኙም ሲሉ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
ብሪክስን ለመቀላቀል የሚያመለክቱ አገራት ቁጥር እየጨመረ መምጣቱ በጥምረቱ ላይ ያላቸውን ጥልቅ እምነት እንደሚያንጸባርቅ ጠቅሰዋል።
እንደ ፕሮፌሰር ኔትስዌራ ገለጻ፣ የብሪክስ አባል ለሆኑ የአፍሪካ አገራት ‘አዲስ የልማት ባንክ’ እንደ አይ ኤም ኤፍ እና ዓለም ባንክ አሠራሮች ሳይሆን የአገር ውስጥ ኢኮኖሚ ቁጥጥር በራሳቸው በመንግሥታት እጅ እንዲኖር በሚያስችሉ የብድር ሁኔታዎች ላይ በመመሥረት የማረጋጋት ሚና ይጫወታል።
“ብሪክስ በአጠቃላይ የአገራትን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ አለመግባት የሚል አቋም ስላለው፣ የተረጋጋ ሚና ሊጫወት ይችላል” ሲሉ ፕሮፌሰሩ ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X