አፍሪካውያን በአሜሪካ ባዮሎጂካል ሙከራዎች ውስጥ ሁል ጊዜም እንደ ‘ጥናት ቁሳቁስ’ ሲያገለግሉ ቆይተዋል - ደቡብ አፍሪካዊ ባለሙያ

ሰብስክራይብ

አፍሪካውያን በአሜሪካ ባዮሎጂካል ሙከራዎች ውስጥ ሁል ጊዜም እንደ ‘ጥናት ቁሳቁስ’ ሲያገለግሉ ቆይተዋል - ደቡብ አፍሪካዊ ባለሙያ

አሜሪካ በውጭ አገራት የሚገኙ ባዮላቦራቶሪዎቿ ላይ ምርመራ የጀመረችው “አሁን ላይ አመኔታዋ አደጋ ላይ ስለወደቀ ነው” ሲሉ በትሽዋኔ የቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሀብት ታሪክ እና የልማት ሶሺዮሎጂ ባለሙያ የሆኑት ዶክተር ብሌሲንግ ካሩምቢድዛ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

“የእኛ ሕማም የሚታየው የአሜሪካን ፍላጎት እና የአሜሪካን ኃይል አደጋ ላይ በሚጥልበት ጊዜ ብቻ ነው። ስለዚህ፣ ከአፍሪካውያን እይታ አንጻር የአሜሪካ ምርመራ ስለ ሳይንስ ብቻ ሳይሆን ስለ ኃይል/ተፅዕኖ ጭምር ነው፤ ምክንያቱም ለአሥርት ዓመታት የአፍሪካውያን አካል ለምዕራባውያን ሙከራዎች እንደ ላቦራቶሪ ሲያገለግል ቆይቷል” ሲሉ ጠቅሰዋል።

እነዚህ ሙከራዎች የአፍሪካን ባዮ-ደህንነት እና ሉዓላዊነት በእጅጉ የሚፈታተኑ መሆናቸውን የገለጹት ተናጋሪው፣ ምክንያቱም እንዲህ ዓይነቶቹ ጥናቶች “የኢምፔሪያሊዝምን እውቀት የሚያስቀጥሉ ናቸው” ሲሉ አፅንዖት ሰጥተዋል።

“ይህ ሳይንሳዊ ነፃነት የሌለው ሉዓላዊነት አፍሪካን ለብዝበዛ ተጋላጭ ያደርጋታል” ሲሉም አሳስበዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0