የዶላርን የበላይነት ለመገዳደር ከስዊፍት ውጪ ያሉ አማራጭ የክፍያ ሥርዓቶች መዘርጋት አለባቸው - ተንታኝ
16:50 16.05.2026 (የተሻሻለ: 16:54 16.05.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የዶላርን የበላይነት ለመገዳደር ከስዊፍት ውጪ ያሉ አማራጭ የክፍያ ሥርዓቶች መዘርጋት አለባቸው - ተንታኝ
እንደ ደቡብ አፍሪካዊው ተንታኝ ራሲጋን ማሃራጅ ገለጻ፣ በብሔራዊ ገንዘቦች የመገበያየት አዝማሚያ እያደገ የመጣ ሲሆን ይህ ይበልጥ ሊበረታታ ይገባል።
ይሁን እንጂ የዓለም አቀፍ መጠባበቂያ ገንዘብ ባለቤት የሆነችው ሀገር ይህንን ዕድል እንደ መሣሪያ እየተጠቀመችበት መሆኑን ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
አሜሪካ ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርቷ ከ143% በላይ የሆነ የሀገር ውስጥ ዕዳ እንዳለባትና የስዊፍት ሥርዓትን ለሁሉም እኩል ተደራሽ ማድረግ እንደማይቻል በተግባር መታየቱን ጠቅሰዋል።
ባለብዙ-ዋልታ የዓለም ሥርዓትን ለማስፈን ፍላጎት ባላቸው ወገኖች መካከል አማራጭ የክፍያ ሥርዓቶች ሊገነቡ እንደሚችሉና መገንባትም እንዳለባቸው ማሃራጅ ሞግተዋል።
“በአፍሪካ የሚደረጉ ጥረቶች ከክፍያ ሥርዓቶች ባለፈ ጥልቅ የሆኑ የፋይናንስ ኢ-ፍትሐዊነቶችን ለመቅረፍ መዘርጋት አለባቸው። ይህም ፍትሐዊ ያልሆኑ የብድር ምዘናዎችን፣ የካፒታል ወጪን የመወሰን አድሎአዊ አሰራሮችን እና ከአኅጉሪቱ የሚወጡ ሕገ-ወጥ የገንዘብ ፍሰቶችን ማስቆምን ያጠቃልላል” ሲሉ ሀሳባቸውን ደምድመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X