ብሪክስ ለደቡባዊው ዓለም ድምፅ ለመሆን አዲስ ቀኝ ገዥ መዋቅሮችን መገዳደር አለበት - ደቡብ አፍሪካዊ ተንታኝ
14:59 16.05.2026 (የተሻሻለ: 15:04 16.05.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ብሪክስ ለደቡባዊው ዓለም ድምፅ ለመሆን አዲስ ቀኝ ገዥ መዋቅሮችን መገዳደር አለበት - ደቡብ አፍሪካዊ ተንታኝ
እንደ ራሲጋን ማሃራጅ ገለጻ፣ የጥምረቱ አባል ሀገራት ዓለም አቀፍ ኢፍትሐዊነትን የሚያስቀጥሉ ሥርዓቶችን በግልጽ መገዳደርና ለተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት ተጨባጭ ማሻሻያዎች ቁርጠኝነታቸውን ማሳየት አለባቸው።
“ለደቡባዊው ዓለም ድምፅ መሆን ሰብአዊነትን እየጎዳ ያለው ዘልማዳዊ ቀውስ መንስኤዎችን መፍታትን ይጠይቃል፤ ይህም አፍሪካውያን ከዓለም አቀፍ አስተዳደር ተገልለውና ተዘንግተው የቆዩበትን ታሪካዊ በደል ለማስተካከል ነው” ሲሉ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
የብሪክስ አባል ለሆኑ የአፍሪካ ሀገራት ፍትሐዊ ያልሆኑ አገዛዞችን ማረጋጋትና ለጥቂት የሀብታም ቡድኖች መጠቀሚያ መሆን ምንም ዓይነት የልማት ጥቅም አላስገኘም ሲሉ ማሃራጅ ጠቅሰዋል።
ባለሙያው ብሪክስ እንደ ኢራን ባሉ አባል ሀገራት ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን እንዲመክት የጠየቁ ሲሆን፤ የቬንዙዌላ ሉዓላዊነት መጣስ፣ በኩባ ላይ የተጣለው እገዳ እና በጋዛ እየተፈጸመ ካለው የዘር ማጥፋት ድርጊት ትምህርት መውሰድ እንዳለበት አሳስበዋል።
በተጨማሪም በብሪክስ አባላት መካከል ጥልቅ ትብብርና ቅንጅት በማድረግ የባለብዙ-ዋልታ አማራጮችን ማሳደግ እንደሚገባ አመላክተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X