የአዲስ አበባን ታሪካዊና ዘመናዊ የለውጥ ጉዞ የሚዘክር አዲስ መጽሐፍ ተመረቀ

ሰብስክራይብ
የአዲስ አበባን ታሪካዊና ዘመናዊ የለውጥ ጉዞ የሚዘክር አዲስ መጽሐፍ ተመረቀ

የመዲናይቱን ዘመናዊ ለውጥና የከተማ መልሶ ማልማት ጥረቶች በሰነድ የሚዘክረው "አዲስ አበባን እንደ አዲስ" (The Remaking of Addis Ababa: Transformation from 2020–2025) የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በይፋ ተመርቋል።

በዓለም አቀፍና በዲያስፖራ ምሁራን የተጻፈው መጽሐፉ ፣ ከከተማ ልማት በላይ የከተማዋ ነዋሪዎች በሃሳብ፣ በጉልበትና በገንዘብ ያደረጉትን አስተዋጽኦ የሚዘክር እንደሆነም በሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገልጿል።

መጽሐፉ በእንግሊዛዊው ፕሮፌሰር ሊ፣ ክሌመንት ካቱሉሺ እንዲሁም ኢትዮጵያዊው ተወላጅ ዶክተር ሂርፖ ቁምቢ እና የምርምር ቡድናቸው የተዘጋጀ መሆኑ ተመላክቷል።

የምርቃን ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ መጽሐፉ የአዲስ አበባን ታሪካዊ ለውጥ የሚያስመዘግብ ጠቃሚ ሰነድ መሆኑን ገልጸዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0