“የአፍሪካ የትምህርት ሥርዓት ከቅኝ ግዛት እሳቤ ነፃ መውጣት አለበት” – ባለሙያ

ሰብስክራይብ

“የአፍሪካ የትምህርት ሥርዓት ከቅኝ ግዛት እሳቤ ነፃ መውጣት አለበት” – ባለሙያ

የአኅጉሪቱ ሥርዓት ትምህርቶች አካባቢያዊ ተሞክሮዎችን እና ሀገር በቀል እውቀቶችን ማካተት እንዳለባቸው የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ ቀነኒሳ ለሚ (ዶ/ር) ከአፍሪካ የቢዝነስ ትምህርት ቤቶች ማኅበር ዓመታዊ ጉባኤ ጎን ለጎን ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

ዋና ጸሐፊው "የትምህርት ሥርዓቶቻችን ከሀገር ውስጥ ተጨባጭ ሁኔታ ጋር ሳይጣጣሙ ከውጭ የተቀዱ ናቸው። ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጭምር ተማሪዎቻቸውን በመሬት ላይ ካለው ተጨባጭ ሁኔታ ጋር ሳያስተዋውቁ ንድፈ ሃሳቦችን ብቻ ያስተምራሉ። ለዚህም ነው ሁላችንም በንድፈ ሃሳቦች ውስጥ ብቻ አልፈን ከዩኒቨርሲቲ ከተመረቅን በኋላ ለተጨባጭ ሁኔታዎች የምንጋለጠው" ብለዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0