ፕሬዚዳንት ትራምፕ ቻይና እና አሜሪካ የንግድ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስታወቁ
16:07 15.05.2026 (የተሻሻለ: 16:14 15.05.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ፕሬዚዳንት ትራምፕ ቻይና እና አሜሪካ የንግድ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስታወቁ
በትራምፕ የቻይና ጉብኝት የተነሱ አንኳር ሃሳቦች፦
ትራምፕ ሺ ጂንፒንግን “ወዳጅ” ሲሉ በመጥራት፤ ለቻይናው መሪ ጥልቅ አክብሮት እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡
ሁለቱ ሀገራት "በጣም ጥሩ የንግድ ስምምነቶች" ላይ መድረሳቸውን አመልክተዋል።
ሺ ጂንፒንግ በበኩላቸው፤ የትራምፕ ይፋዊ የቻይና ጉብኝት ታሪካዊ እና ትርጉም ያለው እንደሆነ አንስተዋል።
ቻይና እና አሜሪካ የተረጋጋ የንግድ ግንኙነታቸውን ለመቀጠል እና በሁሉም ዘርፎች ትብብራችውን ለማስፋፋት መግባባት ላይ መድረሳቸውን የቻይናው ፕሬዚዳንት ጠቁመዋል።
ትራምፕ፤ ቻይና በአሜሪካ ኩባንያዎች ውስጥ በመቶ ቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር ኢንቨስት ለማድረግ ዝግጁ ናት ብለዋል።
የትራምፕ የቻይና ጉብኝት የጋራ መግባባትን ለማሳደግ፣ መተማመንን ለማጠናከር እና የሁለቱንም ሀገራት ሕዝቦች ደህንነት ለማሻሻል አስተዋፅኦ ይኖረዋል ሲሉ ሺ ጂንፒንግ ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X