ዚምባብዌ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከማዕድን 1 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ሽያጭ አስመዘገበች
19:40 14.05.2026 (የተሻሻለ: 19:44 14.05.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ዚምባብዌ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከማዕድን 1 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ሽያጭ አስመዘገበች
የማዕድን ዘርፉ በ2026 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት 983.85 ሚሊዮን ዶላር ገቢ አስገኝቷል። ይህ ስኬት የተመዘገበው መንግሥት ጥሬ ማዕድናት ወደ ውጭ እንዳይወጡ በመከልከሉና በሀገር ውስጥ እንዲቀነባበሩ በመደረጉ እንደሆነ የዚምባብዌ የማዕድን ግብይት ኮርፖሬሽን ገልጿል።
ከፍተኛ የሽያጭ ዕድገት ያስመዘገቡ ማዕድናት (ካለፈው ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ጋር ሲነጻጸር)፦
ሊቲየም፦ 178.64 ሚሊዮን ዶላር (በዋጋ +106 በመቶ፣ በመጠን +2 በመቶ)
የፕላቲኒየም ብረቶች፦ 543.97 ሚሊዮን ዶላር (የተቀነባበሩ ሽያጭ፣ በዋጋ +319 በመቶ፣ በመጠን +98 በመቶ፤ የቀለጠ በዋጋ +69 በመቶ)
የብረት ምርቶች፦ 68.22 ሚሊዮን ዶላር (በዋጋ +254 በመቶ፣ በመጠን +150 በመቶ)
የድንጋይ ከሰል እና ኮክ፦ 50.77 ሚሊዮን ዶላር (በመጠን +30 በመቶ)
ፌሮክሮም እና ፌሮ-አሎይስ፦ 65.81 ሚሊዮን ዶላር (የተረጋጋ ዋጋ እና ምቹ የምርት ቅንጅት)
እንደ ኮርፖሬሽኑ ገለጻ፤ ዚምባብዌ ለዓለም አቀፍ የባትሪ አምራቾች ቁልፍ አጋር እየሆነች መምጣቷን ተከትሎ ዓመታዊ የሊቲየም ገቢዋ ከ1 ቢሊዮን ዶላር ይልቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X