አልጄሪያ ከሩሲያ ጋር በቴክኖሎጂ ዘርፍ ትብብር ለመፍጠር ማቀዷን የሀገሪቱ ሚኒስትር አስታወቁ

ሰብስክራይብ

አልጄሪያ ከሩሲያ ጋር በቴክኖሎጂ ዘርፍ ትብብር ለመፍጠር ማቀዷን የሀገሪቱ ሚኒስትር አስታወቁ

አልጄሪያ በሳይበር ደህንነት፣ በዲጂታል መፍትሄዎች እና በሰው ሠራሽ አስተውህሎት ዘርፎች ከሩሲያ ጋር በትብብር ለመሥራት እንደምትፈልግ የዕውቀት ኢኮኖሚ፣ "ስታርታፖች" እና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች ሚኒስትር ኑረዲን ዋዳህ በ "ሩሲያ-እስላማዊው ዓለም ካዛን ፎረም" ላይ ገልጸዋል።

“በዋናነት ትኩረታችን በሳይበር ደህንነት እና በዲጂታል መፍትሄዎች ላይ ነው። በአሁኑ ወቅት ትልቅ ትኩረት በሚሰጠው የሳይበር ደህንነት ዘርፍ ላይ የጋራ ትብብር ማድረግ እንፈልጋለን” ብለዋል።

የአልጄሪያ ወጣት እና የተማረ የሰው ኃይል እንዲሁም ዝቅተኛ የኢነርጂ ወጪ ለሰፊ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ እና የሰው ሠራሽ አስተውህሎት ትብብር ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ገልጸዋል።

“አልጄሪያን ለሰው ሠራሽ አስተውህሎት እንዲሁም ለዳታ ማዕከልነት መጠቀም ለሩሲያ ጥሩ ዕድል ነው” ሲሉ ዋዳህ አክለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0