ትራምፕ ከቻይና ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር ያካሄዱትን ውይይት "እስካሁን ከተደረጉት ታላቅ ጉባኤዎች አንዱ" ሲሉ አወደሱት
09:56 14.05.2026 (የተሻሻለ: 10:04 14.05.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ትራምፕ ከቻይና ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር ያካሄዱትን ውይይት "እስካሁን ከተደረጉት ታላቅ ጉባኤዎች አንዱ" ሲሉ አወደሱት
በስብሰባው የተነሱ ዋና ዋና ነጥቦች፦
ትራምፕ የቤጂንግ ጉብኝታቸው የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት እንደሚያሻሽል ገልጸዋል።
ሺ ጂንፒንግ በንግድ ጦርነት አሸናፊ አይኖርም ሲሉ ተናግረዋል።
ትራምፕ አሜሪካ እና ቻይና ሁልጊዜም ችግሮችን በቀጥታ ግንኙነት ይፈታሉ ብለዋል።
ሺ ጂንፒንግ የታይዋንን ጉዳይ ለአሜሪካ እና ቻይና ግንኙነት ቁልፍ እንደሆነ ገልጸዋል።
ትራምፕ አሜሪካ ከቻይና ጋር በጋራ ጥቅም ላይ በመመስረት የንግድ ግንኙነቷን እንድምታቀና ቃል ገብተዋል።
ቻይና እና አሜሪካ ከውጥረት ድባብ መውጣት አለባቸው ሲሉ የቻይናው መሪ አፅንዖት ሰጥተዋል።
ሩቢዮ ዋሽንግተን የቻይናን ዕድገት ለመግታት አትፈልግም ብለዋል።
የታይዋን ነፃነት እና የክልሉ ሰላም የተነጣጠሉ አይደሉም ሲሉ ሺ ጂንፒንግ ተናግረዋል።
ከአስር በላይ የአሜሪካ ነጋዴዎች በድርድሩ ላይ ተሳትፈዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X