የዳንጎቴ ማጣሪያ በሚያዝያ ወር 1.66 ቢሊዮን ሊትር ነዳጅ ወደ ውጭ ላከ
14:47 13.05.2026 (የተሻሻለ: 14:54 13.05.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የዳንጎቴ ማጣሪያ በሚያዝያ ወር 1.66 ቢሊዮን ሊትር ነዳጅ ወደ ውጭ ላከ
ይህ የወጪ ንግድ ዕድገት በአሜሪካ እና ኢራን ውጥረት ሳቢያ የነዳጅ አቅርቦት ስጋት ባለበት ወቅት የመጣ ሲሆን ማጣሪያው የላካቸው የነዳጅ ምርቶች የሚከተሉት ናቸው፦
◻ 513 ሚሊዮን ሊትር ቤንዚን፣
◻ 534 ሚሊዮን ሊትር ናፍጣ፣
◻ 615 ሚሊዮን ሊትር የጄት ነዳጅ።
በቀን 650 ሺህ በርሜል የማጣራት አቅም ያለውና በሥራ ላይ የሚገኘው ብቸኛ የናይጄሪያ ግዙፍ የነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካ፤ በመጋቢት ወር 434 ሚሊዮን ሊትር ቤንዚን የወጪ ንግድ በማስመዝገብ ናይጄሪያ ከአስርት ዓመታት በኋላ የተጣራ የቤንዚን ላኪ እንድትሆን አድርጓታል።
በአሜሪካ እና ኢራን ስምምነት ላይ አለመድረስ የሆርሙዝ ባሕር ወሽመጥ ደህንነት ስጋት ላይ መውደቁን ተከትሎ ልክ እንደ ናይጄሪያ፤ በአውሮፓ፣ በአፍሪካ እና በእስያ ካሉ አማራጭ አቅራቢዎች የነዳጅ ፍላጎት ከፍ ብሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X