የዳንጎቴ ማጣሪያ በሚያዝያ ወር 1.66 ቢሊዮን ሊትር ነዳጅ ወደ ውጭ ላከ

© telegram sputnik_ethiopiaየዳንጎቴ ማጣሪያ በሚያዝያ ወር 1
የዳንጎቴ ማጣሪያ በሚያዝያ ወር 1 - Sputnik አፍሪካ, 1920, 13.05.2026
ሰብስክራይብ

የዳንጎቴ ማጣሪያ በሚያዝያ ወር 1.66 ቢሊዮን ሊትር ነዳጅ ወደ ውጭ ላከ

​ ይህ የወጪ ንግድ ዕድገት በአሜሪካ እና ኢራን ውጥረት ሳቢያ የነዳጅ አቅርቦት ስጋት ባለበት ወቅት የመጣ ሲሆን ማጣሪያው የላካቸው የነዳጅ ምርቶች የሚከተሉት ናቸው፦

◻ ​513 ሚሊዮን ሊትር ቤንዚን፣

◻ 534 ሚሊዮን ሊትር ናፍጣ፣

​615 ሚሊዮን ሊትር የጄት ነዳጅ።

​ በቀን 650 ሺህ በርሜል የማጣራት አቅም ያለውና በሥራ ላይ የሚገኘው ብቸኛ የናይጄሪያ ግዙፍ የነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካ፤ በመጋቢት ወር 434 ሚሊዮን ሊትር ቤንዚን የወጪ ንግድ በማስመዝገብ ናይጄሪያ ከአስርት ዓመታት በኋላ የተጣራ የቤንዚን ላኪ እንድትሆን አድርጓታል።

 

​ በአሜሪካ እና ኢራን ስምምነት ላይ አለመድረስ የሆርሙዝ ባሕር ወሽመጥ ደህንነት ስጋት ላይ መውደቁን ተከትሎ ልክ እንደ ናይጄሪያ፤ በአውሮፓ፣ በአፍሪካ እና በእስያ ካሉ አማራጭ አቅራቢዎች የነዳጅ ፍላጎት ከፍ ብሏል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0