ዛምቢያ ፍትሐዊ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋት አዲስ የጤና ፖሊሲ አፀደቀች

ሰብስክራይብ

ዛምቢያ ፍትሐዊ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋት አዲስ የጤና ፖሊሲ አፀደቀች

​ እ.ኤ.አ ከ2026–2030 የሚዘልቀው ብሔራዊ የጤና ፖሊሲ ዋና ዋና በሽታዎችን ለመቋቋም የታለሙ 28 ግቦችን የያዘ መሆኑን የጤና ሚኒስትሩ አሌክስ ካታክዌ ተነሳሽነቱ ይፋ በተደረገበት ሥነ-ሥርዓት ላይ ገልጸዋል።

​ፖሊሲው ከሌሎች በሽታዎች በተጨማሪ በኤችአይቪ፣ በወባ እና በሳንባ ነቀርሳ ላይ ትኩረት እንደሚያደርግም አክለዋል።

​ መንግሥት ለጤናው ዘርፍ የሚመደበውን የገንዘብ ድጋፍ በማሣደግ መሠረተ ልማቶችን እንዳስፋፋ እና ተጨማሪ የጤና ባለሙያዎችንም እንደቀጠረ ሚኒስትሩ ጨምረው ገልጸዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0