በደቡብ አፍሪካ በተከሰተው ዓውሎ ነፋስ ምክንያት የሞቱ ሰዎች ቁጥር 10 ደረሰ

ሰብስክራይብ

በደቡብ አፍሪካ በተከሰተው ዓውሎ ነፋስ ምክንያት የሞቱ ሰዎች ቁጥር 10 ደረሰ

 

በጎርፍና ነፋሱ የሚደርሰው ከፍተኛ ጉዳት መቀጠሉን ተከትሎ፤ መንግሥት በስድስት ግዛቶች ውስጥ የተፈጥሮ አደጋ ግዜ አዋጅ አውጇል፡፡ ዌስተርን ኬፕ  በከፍተኛው ከተመቱ ግዛቶች ዋነኛው መሆኑን የአካባቢው መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

ዓውሎ ነፋሱ ያስከተላቸው ዋና ዋና ጥፋቶች፡-

​🟠 በቤቶች እና መሠረተ ልማቶች ላይ የደረሰው ሰፊ ውድመት፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች እንዲፈናቀሉ እና የኤሌክትሪክ ኃይላቸው እንዲቋረጥ አድርጓል፣  

 

​🟠 በርካታ ትምህርት ቤቶች እንዲዘጉ እና መንገዶች፣ የተራራ ማለፊያዎች እና የበረራ ሥራዎችን ጨምሮ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ መስተጓጎል እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል፣

​🟠 በጎርፍ መጥለቅለቅ፣ በወንዞች መፍሰስ እና በግድቦች መደርመስ ስጋት ምክንያት ብዛት ያላቸው ነዋሪዎች አካባቢያቸውን እንዲለቁ ትዕዛዝ ተላልፏል።

​ ሁለተኛውና ይበልጥ ኃይለኛው ቀዝቃዛ አየር ከምዕራብ አቅጣጫ ወደ ደቡብ አፍሪካ እየተቃረበ መሆኑን የሜትሮዎሎጂ ተመራማሪዎች አስጠንቅቀዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0