በኬንያ እየተካሄደ የሚገኘውን የፈረንሳይ ጉባኤ በመቃወም ሰልፎች ተካሄዱ
14:09 12.05.2026 (የተሻሻለ: 14:14 12.05.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በኬንያ እየተካሄደ የሚገኘውን የፈረንሳይ ጉባኤ በመቃወም ሰልፎች ተካሄዱ
ሰልፎቹ በኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ እና በፈረንሳዩ ኢማኑኤል ማክሮን በሚመራው የ "አፍሪካ ፎርዋርድ" ጉባኤ ማጠቃለያ፤ ፓን-አፍሪካኒዝም ሰሚት አጌንስት ኢምፔሪያሊዝም በተሰኘው ድርጅት የተዘጋጁ ናቸው።
በኬንያታ አቬኑ ሰልፈኞች ላይ የአስለቃሽ ጭስ እንደተተኮሰባቸውና በርካቶችም በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የስፑትኒክ አፍሪካ ዘጋቢ ገልጿል።
አክቲቪስቶች በ"ኡፉንጋማኖ ሃውስ" ለተቃውሞ ጉባኤ በመሰባሰብ፤ "ዳግም ቅኝ አገዛዝን" እና በምስራቅ አፍሪካ የፈረንሳይ ወታደራዊ መስፋፋትን ለመቃወም ወደ ኬንያ ዓለም አቀፍ የስብሰባ ማዕከል አቅራቢያ ለመንቀሳቀስ እየሞከሩ ነው።
የሀገሪቱ ብሔራዊ የፖሊስ አገልግሎት በማዕከላዊ የንግድ ዲስትሪክት ከፍተኛ የደህንነት ኃይል በማሰማራት፤ የጉባኤውን ሥፍራ እና የዓለም አቀፍ ተወካዮችን ደህንነት ለመጠበቅ ሲቲ ሆል ዌይ እና ሀራምቤ አቬኑን ጨምሮ ዋና ዋና መንገዶችን ዘግቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X