አፍሪካ ‘የዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት የአደን ግዛት እና የሕግ ሙከራ ላቦራቶሪ አይደለችም’ - ሱዳናዊ ምሁር
10:02 12.05.2026 (የተሻሻለ: 10:04 12.05.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
አፍሪካ ‘የዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት የአደን ግዛት እና የሕግ ሙከራ ላቦራቶሪ አይደለችም’ - ሱዳናዊ ምሁር
በሩሲያ ፋይናንሻል ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ መምህር ዶ/ር መሐመድ ሁሴን አብዱልዋሂድ ለስፑትኒክ አፍሪካ እንደተናገሩት፤ 80 በመቶ የሚሆኑት የዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት (አይሲሲ) ምርመራዎች የአፍሪካ ጉዳዮች ላይ ሲያተኩሩ፤ በሌሎች የዓለም ክፍሎች የተፈጸሙና በሰነድ የተደገፉ የጦር ወንጀሎች ግን በፍርድ ቤቱ ችላ ይባላሉ።
እንደ መምህሩ ገለጻ፤ ይህንን ኢ-ፍትሐዊነት ለመቅረፍ አፍሪካውያን ሀገራት የሚከተሉትን እርምጃዎች መውሰድ ይኖርባቸዋል፦
የአይሲሲ ሂደቶችን የሚከታተል ቋሚ ተቋማዊ አካል በአፍሪካ ኅብረት ውስጥ መፍጠር፣
እንደ ሩሲያ እና ቻይና ካሉ ኃያላን ሀገራት ጋር ያላቸውን ግንኙነት ማጠናከር፣
በራሳቸው የዓለም አቀፍ ሕግ ባለሙያዎች ሥልጠና ላይ ኢንቨስት ማድረግ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X