ደቡብ አፍሪካ ሕይወታቸውን ላጡ የመድፈኛ ጦር ወታደሮች ክብር ሰጠች
20:04 11.05.2026 (የተሻሻለ: 20:14 11.05.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ደቡብ አፍሪካ ሕይወታቸውን ላጡ የመድፈኛ ጦር ወታደሮች ክብር ሰጠች
🪖 እ.ኤ.አ. ግንቦት 10 ቀን 1952 የተመረቀው በፖቸፍስትሩም የሚገኘው የ"ጋነርስ ሜሞሪያል"፤ በሁለቱ የዓለም ጦርነቶች እና ከዚያ በኋላ በነበሩ ግጭቶች ሕይወታቸውን ላጡ የደቡብ አፍሪካ የመድፈኛ ጦር አባላት በሙሉ ክብር የሚሰጥ ሲሆን፣ በየዓመቱ በግንቦት ወር የመታሰቢያ አገልግሎት ይከናወንበታል።
ታሪካዊ ዳራ፦
🟠 መታሰቢያው የቀድሞው አንደኛው የዓለም ጦርነት የመድፈኛ ጦር አባል በነበሩት በዶክተር ጎርደን ሌይዝ የተነደፈ ሲሆን፣ ቀደም ሲል የጦር ሰፈር መግቢያ በነበረ ስፍራ አቅራቢያ ተተክሏል።
🟠 መጀመሪያ ላይ በአንደኛው እና በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ለወደቁ መድፈኞች የተሰየመ ቢሆንም፤ በ1998 ዓ.ም ግን ህጋዊ እና መደበኛ ያልሆኑ ኃይሎችን ጨምሮ ለደቡብ አፍሪካ ሲሉ ህይወታቸውን የሰጡ ሁሉንም መድፈኞች እንዲያዘክር ዳግም ተሰይሟል።
"ለፈጣሪ ክብር እና ለደቡብ አፍሪካ ሕይወታቸውን ለሰጡ መድፈኞች መታሰቢያ ይሁን" ይላል በማስታወሻው ላይ የተታተመው ተጨማሪ ጽሑፍ።
🟠 የመታሰቢያ ሀውልቱ የደቡብ አፍሪካ የመድፈኞች ማህበር ጥረት ውጤት ሲሆን፤ ማህበሩ በራዕዩ እንደገለጸው "የመድፈኛ ጦር ወጎችን ለማስፋፋት እና ቅርሶችን ለመጠበቅ" ይሰራል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X