- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

ዓለም አቀፍ የነዳጅ ቀውስ እና የኢትዮጵያ የስትራቴጂካዊ አማራጮች ፍለጋ

ዓለም አቀፍ የነዳጅ ቀውስ እና የኢትዮጵያ የስትራቴጂካዊ አማራጮች ፍለጋ
ሰብስክራይብ
“ከውጭ ነዳጅ ጥገኝነት ለመውጣት የተቀናጀ ስትራቴጂ ያስፈልጋል። ትኩረታችንን የኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማትን በማዘመን፣ በፀሐይ ኃይል እና በአገር ውስጥ የተፈጥሮ ጋዝ ምርት ላይ በማድረግ የኢነርጂ ሉዓላዊነታችንን ማረጋገጥ ይኖርብናል።” ሲሉ በኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት (PSI) ወስጥ ከፍተኛ ተመራማሪ የሆኑት ዶ/ር ጀማል መሀመድ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡
ከነዳጅ ፖለቲካ እስከ ቀጠናዊ ደህንነት፦ ኢትዮጵያ በአዲሱ የዓለም የኃይል አሰላለፍ ውስጥ!
በዛሬው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅታችን ሁለት አንገብጋቢ ጉዳዮችን ከባለሙያዎች ጋር በጥልቀት እንመረምራለን፦
የነዳጅ ጂኦ-ፖለቲካ እና የኢትዮጵያ ፈተና፦ የዓለም የነዳጅ ገበያ አለመረጋጋት በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ የሚፈጥረውን ጫና እና ሀገሪቱ የጀመረችው የጋዝ ተሽከርካሪዎች (Natural Gas Conversion) ሽግግር እንደ መፍትሄ ሊታይ ይችላል? የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት (PSI) ከፍተኛ ተመራማሪ ዶ/ር ጀማል መሀመድ ሰፊ ትንታኔ ይሰጡናል።
የኢትዮጵያ እና ታንዛኒያ ወታደራዊ ትብብር፦ ሽብርተኝነትንና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን ለመከላከል በኢትዮጵያ እና በታንዛኒያ መካከል እየተገነባ ያለው ወታደራዊ ግንኙነት በቀጠናው የኃይል ሚዛን ላይ ምን ለውጥ ያመጣል? የዓለም አቀፍ ጉዳዮች ተንታኙ አብዱልናስር ምዊታ በጉዳዩ ላይ ያላቸውን እይታ ያካፍሉናል።

መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ሙሉ ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple PodcastsSpotifyDeezerAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0