ኢትዮጵያዊው አትሌት ታደሰ ካሳ እሁድ የተካሄደውን የ2026 የኮፐንሃገን ማራቶንን አሸነፈ
17:26 11.05.2026 (የተሻሻለ: 17:34 11.05.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያዊው አትሌት ታደሰ ካሳ እሁድ የተካሄደውን የ2026 የኮፐንሃገን ማራቶንን አሸነፈ
ታደሰ፣ 2:08:26 በማጠናቀቅ የግል የሠዓት ክብረ-ወሰኑን በማሻሻል አሸንፏል።
ኬንያዊው ቪንሴንት ሙታይ፣ 2:08:30 በመግባት ውድድሩን በሁለተኝነት አጠናቋል፡፡
ሌላኛው ኢትዮጵያዊ ደጀኔ ወይፈን በ2:09:14 ሠዓት ሦስተኛ ደረጃን ይዟል።
በሴቶች፦
ኬንያዊቷ መርሲ ቼፕዎገን፣ 2:22:08 በመግባት የመጀመሪያዋን የማራቶን ድል ተቀዳጅታለች፡፡
ባሕሬናዊቷ ትዕግስት ጋሻው፣ በ2:23:07 ሠዓት ሁለተኛ ወጥታለች፡፡
ኢትዮጵያዊቷ ፋንቱ ሹጊ፣ በ2:24:38 ሠዓት ሦስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X