ዚምባብዌ በ294 ሚሊዮን ዶላር የምታከናውነው የካሪባ ግድብ እድሳት 94 በመቶ መድረሱን አስታወቀች
15:44 11.05.2026 (የተሻሻለ: 15:54 11.05.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ዚምባብዌ በ294 ሚሊዮን ዶላር የምታከናውነው የካሪባ ግድብ እድሳት 94 በመቶ መድረሱን አስታወቀች
የዛምቤዚ ወንዝ ባለስልጣን እንደገለጸው፣ የግድቡ እድሳት ስራ እ.ኤ.አ. እስከ 2026 ማብቂያ ድረስ ይጠናቀቃል ተብሎ በታቀደው መርሃ ግብር መሰረት እየተከናወነ ይገኛል።
ፕሮጀክቱ ስድስቱን የግድቡ የውሃ መቆጣጠሪያ በሮች አስተማማኝነት፣ ደህንነት እና ተግባራዊነት ወደ ነበሩበት ለመመለስ የሚያስችል የትርፍ ውሃ መውረጃ እድሳትን ያካትታል።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ሙንያራዚ ሙኖዳዋፋ "በአሁኑ ወቅት ለቁጥር 1፣ 2፣ 5 እና 6 የውሃ መቆጣጠሪያ በሮች የማንሳት ስርዓት የመገጠም ስራ በመከናወን ላይ ይገኛል" ብለዋል።
ይህ የእድሳት መርሃ ግብር ከቁጥጥር ውጪ የሚወጣ የውሃ ፍሰት የሚያስከትለውን የጎርፍ አደጋ፣ የመሰረተ ልማት ውድመት እና የደህንነት ስጋት ለመከላከል ወሳኝ መሆኑን ባለስልጣኑ አክሎ ገልጿል።
በዛምቤዚ ወንዝ ባለስልጣን በኩል የሚከናወነው የዚምባብዌ እና የዛምቢያ የጋራ ጥረት፣ በክልሉ እየጨመረ የመጣውን የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ለማሟላትና የኃይል ምርትን ለማረጋገጥ ያለመ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X