ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ ስምንት ወራት ብቻ ከሥጋ ወጪ ንግድ 87 ሚሊዮን ዶላር ማግኘቷ ተዘገበ
12:25 11.05.2026 (የተሻሻለ: 12:34 11.05.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ ስምንት ወራት ብቻ ከሥጋ ወጪ ንግድ 87 ሚሊዮን ዶላር ማግኘቷ ተዘገበ
የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት በዋነኛነት ሳዑዲ ዓረቢያና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የኢትዮጵያ የሥጋ ምርት መዳረሻ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ሥጋ አምራችና ላኪዎች ማኅበር አስታውቋል፡፡
የአፍሪካ አኅጉር አቀፍ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነትን ተከትሎ ወደ ጋና እና ሶማሊያ ምርት እየተላከ መሆኑን የገለፁት የመኅበሩ ፕሬዝዳንት ከሊፋ ሁሴን፣ የሥጋ ተረፈ ምርት ደሞ ወደ ቬትናም እና ሆንግ ኮንግ እንደሚላክ ጠቁመዋል።
በዘርፉ ላይ የተደረጉ ማሻሻያዎችን ተከትሎ ወደ ውጭ የሚላክ የስጋ ምርት በመጠንና በገቢ በከፍተኛ መጠን ማደጉንም ፕሬዝዳንቱ ለሀገር ውስጥ ሚድያ ገልፀዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X