ኢትዮጵያና ናይጄሪያ ድንበር ተሻጋሪ የግብርና ምርት ንግድ እና ፋይናንስ ለማሳደግ ተስማሙ

ኢትዮጵያና ናይጄሪያ ድንበር ተሻጋሪ የግብርና ምርት ንግድ እና ፋይናንስ ለማሳደግ ተስማሙ
ኢትዮጵያና ናይጄሪያ ድንበር ተሻጋሪ የግብርና ምርት ንግድ እና ፋይናንስ ለማሳደግ ተስማሙ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 10.05.2026
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያና ናይጄሪያ ድንበር ተሻጋሪ የግብርና ምርት ንግድ እና ፋይናንስ ለማሳደግ ተስማሙ

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ እና የናይጄሪያ የግብርና ብድር ስጋት መጋሪያ ተቋም፣ የግብርና ምርት ግብይት ሥርዓትን ለማዘመንና ድንበር ተሻጋሪ ንግድን ለማጠናከር የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

በአዲስ አበባ የተፈረመው ይህ የመግባቢያ ሰነድ፤ በጋራ መጋዘን ደረሰኝ ፋይናንስ፣ በምርት ጥራት ቁጥጥር፣ በዲጂታል የንግድ መሠረተ ልማት እና በቴክኒክ ዕውቀት ሽግግር ዙሪያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ነው።

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መርጋ ባይሳ፤ ስምምነቱ ግልጽና ቀልጣፋ የግብርና ምርት ገበያ ለመፍጠርና የአምራቾችን የብድር አቅርቦት በማሻሻል፤ አፍሪካውያን በአኅጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ማዕቀፍ ውስጥ ያላቸውን የንግድ ትስስር ይበልጥ ያጠናክረዋል ብለዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0