“የኢትዮጵያና የጅቡቲ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለቀጣናችን ሰላምና መረጋጋት መጠናከር መሠረት ነው” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

የኢትዮጵያና የጅቡቲ ስትራቴጂካዊ አጋርነት
የኢትዮጵያና የጅቡቲ ስትራቴጂካዊ አጋርነት - Sputnik አፍሪካ, 1920, 09.05.2026
ሰብስክራይብ
“የኢትዮጵያና የጅቡቲ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለቀጣናችን ሰላምና መረጋጋት መጠናከር መሠረት ነው” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

በፕሬዝዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌ በዓለ ሲመት ሥነ-ሥርዓት ለመታደም ዛሬ ጅቡቲ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የቆየ ወዳጅነት እና ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለሕዝቦች የጋራ ብልጽግና መጎልበት የላቀ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል።

ፕሬዝዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌ በድጋሚ በመመረጣቸው የተሰማቸውን ልባዊ ደስታ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ፕሬዝዳንቱ ለሀገራቸው የሚሰጡት አገልግሎት የጅቡቲን ሁለንተናዊ እድገት እንደሚያስቀጥል ያላቸውን እምነትም በማኅበራዊ ሚዲያቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት ላይ አክለዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0