የአፍሪካ የገንዘብ ተቋም ለአኅጉራዊው የጋራ መገበያያ ገንዘብ መንገድ ጠራጊ ለመሆን በመስከረም 2026 ሥራ ሊጀምር ነው
18:10 08.05.2026 (የተሻሻለ: 18:22 08.05.2026)

ሰብስክራይብ
የአፍሪካ የገንዘብ ተቋም ለአኅጉራዊው የጋራ መገበያያ ገንዘብ መንገድ ጠራጊ ለመሆን በመስከረም 2026 ሥራ ሊጀምር ነው
የአፍሪካ ማዕከላዊ ባንክን ለማቋቋም እና አኅጉራዊ የጋራ መገበያያ ገንዘብን ስራ ላይ ለማዋል እንደ ሽግግር አካል ሆኖ የሚያገለግለው "የአፍሪካ የገንዘብ ተቋም" እ.አ.አ. በመስከረም 2026 ስራ እንደሚጀምር ተገልጿል። ይህ ይፋ የተደረገው በዳካር በተካሄደው የአፍሪካ ማዕከላዊ ባንኮች ማህበር ቢሮ ስብሰባ ላይ ነው።
የማህበሩ ፕሬዝዳንት ኢቮን ሳና ባንጉዪ እንደገለጹት፣ የተቋሙ መቋቋም ለአፍሪካ የገንዘብ እና የፋይናንስ ውህደት ወሳኝ እርምጃ ነው።
የተቋሙ ደንብ በየካቲት 8 ቀን በአፍሪካ ህብረት የመንግስታት እና የርዕሰ ብሄሮች ጉባኤ የጸደቀ ሲሆን፣ ዋና መሥሪያ ቤቱም በአቡጃ፣ ናይጄሪያ እንደሚሆን ታውቋል።
የአፍሪካ ማዕከላዊ ባንኮች ማህበር 41 ማዕከላዊ ባንኮችን በአባልነት የያዘ ሲሆን፣ በተለይም በ"አጀንዳ 2063" ስር ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ጋር በቅርበት ይሰራል ተብሏል። ኃላፊዎቹ እስከ መስከረም ወር ድረስ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት አባል ባንኮች ለተቋሙ ዝግጅት ንቁ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
ባለሙያዎቹ፣ ተቋሙ አኅጉሪቱ ካላት የማክሮ ኢኮኖሚ ትስስር ምኞት ጋር የሚመጣጠን በቂ ግብዓት ሊሟላለት ይገባል ሲሉ አጽንዖት ሰጥተው ገልፀዋል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
የአፍሪካ ማዕከላዊ ባንክን ለማቋቋም እና አኅጉራዊ የጋራ መገበያያ ገንዘብን ስራ ላይ ለማዋል እንደ ሽግግር አካል ሆኖ የሚያገለግለው "የአፍሪካ የገንዘብ ተቋም" እ.አ.አ. በመስከረም 2026 ስራ እንደሚጀምር ተገልጿል። ይህ ይፋ የተደረገው በዳካር በተካሄደው የአፍሪካ ማዕከላዊ ባንኮች ማህበር ቢሮ ስብሰባ ላይ ነው።
የማህበሩ ፕሬዝዳንት ኢቮን ሳና ባንጉዪ እንደገለጹት፣ የተቋሙ መቋቋም ለአፍሪካ የገንዘብ እና የፋይናንስ ውህደት ወሳኝ እርምጃ ነው።
የተቋሙ ደንብ በየካቲት 8 ቀን በአፍሪካ ህብረት የመንግስታት እና የርዕሰ ብሄሮች ጉባኤ የጸደቀ ሲሆን፣ ዋና መሥሪያ ቤቱም በአቡጃ፣ ናይጄሪያ እንደሚሆን ታውቋል።
የአፍሪካ ማዕከላዊ ባንኮች ማህበር 41 ማዕከላዊ ባንኮችን በአባልነት የያዘ ሲሆን፣ በተለይም በ"አጀንዳ 2063" ስር ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ጋር በቅርበት ይሰራል ተብሏል። ኃላፊዎቹ እስከ መስከረም ወር ድረስ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት አባል ባንኮች ለተቋሙ ዝግጅት ንቁ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
ባለሙያዎቹ፣ ተቋሙ አኅጉሪቱ ካላት የማክሮ ኢኮኖሚ ትስስር ምኞት ጋር የሚመጣጠን በቂ ግብዓት ሊሟላለት ይገባል ሲሉ አጽንዖት ሰጥተው ገልፀዋል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X