ቻድ በላክ ግዛት በደረሰ የሽብር ጥቃት ሳቢያ ብሔራዊ ሀዘን ላይ ናት
13:38 08.05.2026 (የተሻሻለ: 13:44 08.05.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ቻድ በላክ ግዛት በደረሰ የሽብር ጥቃት ሳቢያ ብሔራዊ ሀዘን ላይ ናት
በቦኮ ሀራም* ታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት ለተገደሉ ወታደሮች መታሰቢያ እንዲሆን ከግንቦት 6 እስከ 9 ቀን 2026 የሚቆይ የሦስት ቀናት ብሔራዊ ሀዘን ታውጇል።
ሰንደቅ ዓላማዎች ዝቅ ተደርገው እንዲውለበለቡ የተወሰነ ሲሆን ማንኛውም የበዓል እና የደስታ እንቅስቃሴዎች መታገዳቸውን የስፑትኒክ አፍሪካ ዘጋቢ ዘግቧል፡፡
እንደ ወታደራዊ ዕዝ መግለጫ ከሆነ፣ ከግንቦት 4 እስከ 5 ቀን 2026 ሌሊት በባርካ ቶሎሮም ደሴት ላይ በተፈጸመው በዚህ ጥቃት 23 ሰዎች ሲገደሉ 26ቱ ደግሞ ቆስለዋል።
ጥቃቱን የፈጸሙት ታጣቂዎች የተደመሰሱ ሲሆን የተለያዩ ወታደራዊ ቁሳቁሶችንም መያዝ ተችሏል።
*በሩሲያ የታገደ የሽብር ድርጅት
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X