የተዝናኖት ምሽት፦ የአፍሪካ ማኅበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የአራዳ ፓርክ ጉብኝት

ሰብስክራይብ
የተዝናኖት ምሽት፦ የአፍሪካ ማኅበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የአራዳ ፓርክ ጉብኝት

ዛሬ፣ የአፍሪካን እውነተኛ ገጽታ ለዓለም ለማስተዋወቅና የዲጂታል ትርክቱን በባለቤትነት ለመምራት ያለመው የመጀመሪያው የአፍሪካ ማኅበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ በአዲስ አበባ ዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ነው።

በጉባኤው ለመታደም ከ30 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ 321 ሚሊዮን በላይ የማኅበራዊ ሚዲያ ተከታዮች ያላቸው 61 ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አዲስ አበባ ይገኛሉ፡፡ በተጨማሪም 150 ሚሊዮን ተከታዮች ያላቸው 120 ኢትዮጵያውያን የይዘት ፈጣሪዎች በጉባኤው እንደሚሳተፉ ቱሪዝም ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

በትናትናው ዕለት፣ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን፣ የመዲናዋን በተለያዩ የልማት ሥራዎች እና አመሻሽ ላይ በቅርቡ የተመረቀውን አራዳ ፓርክን ጎብኝተዋል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0