ከውጭ የሚገቡ የግብርና ግብዓቶች 'የቡሩንዲን አፈር እያወደሙ ነው' – የግብርና ባለሙያ

ሰብስክራይብ

ከውጭ የሚገቡ የግብርና ግብዓቶች 'የቡሩንዲን አፈር እያወደሙ ነው' – የግብርና ባለሙያ

ከውጭ የሚገቡ ማዳበሪያዎች እና ፀረ-ተባይ መድኃኒቶች የአፈርን አሲዳማነት ከመጨመራቸውም በላይ ለዕፅዋት እድገት ጠቃሚ የሆኑ ለዐይን የማይታዩ ጥቃቅን ሕዋሳት እንደሚገድሉ የቡሩንዲ የተፈጥሮአዊ (ኦርጋኒክ) ግብርና ንቅናቄ ፕሬዝዳንት አድሪያን ሲቦማና ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል።

"እነዚህ ግብዓቶች በቀላሉ መተው እንችላለን፤ አካባቢን የሚጠብቅና በትክክል ከተከናወነም ትርፋማ የሆነ ግብርናን በቀላሉ መተግበር እንችላለን። መፍትሔው ተፈጥሮአዊ ግብርና ነው። የአፍሪካ ሀገራት በምግብ ራሳቸውን ለመቻል ከፈለጉ፣ በአካባቢው የሚገኙ ተተኪ ግብዓቶች እያሉ ራሳቸው ያላመረቷቸውን የውጭ ምርቶች በማስገባት ማረስ የለባቸውም" ሲሉ ገልጸዋል።

የአፍሪካ ሕብረት እ.ኤ.አ. በ2000ዎቹ የተፈጥሮ ግብርናን የቀዳሚነት ትኩረት እንዲያገኝ መወሰኑንም ተናጋሪው አክለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0