የናይጄሪያው የግዙፍ ኩባንያ ባለቤት በአፍሪካ ሁለተኛው ባለሀብት ሆኑ - መገናኛ ብዙኃን
18:47 07.05.2026 (የተሻሻለ: 19:11 07.05.2026)
© Sputnik
ሰብስክራይብ
የናይጄሪያው የግዙፍ ኩባንያ ባለቤት በአፍሪካ ሁለተኛው ባለሀብት ሆኑ - መገናኛ ብዙኃን
የ"ቢዩኤ" ግሩፕ መሥራች እና ሊቀመንበር አብዱል ሳማድ ራቢው የሀብት መጠናቸው በግምት 19 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር መድረሱ ተዘግቧል። ይህም ከአሊኮ ዳንጎቴ በመቀጠል በአፍሪካ ሁለተኛው ባለጸጋ ያደርጋቸዋል።
ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ ብቻ ሀብታቸው በ8.88 ቢሊዮን ዶላር የጨመረ ሲሆን፣ ይህም በአኀጉሪቱ ካሉ ቢሊየነሮች መካከል ከፍተኛው የሀብት ዕድገት መሆኑን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ለዚህ አስደናቂ የሀብት ዕድገት ሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ተጠቃሽ ናቸው፦
ቢዩኤ ሲሚንቶ - በአፍሪካ ካሉ ግዙፍ የሲሚንቶ አምራቾች አንዱ መሆኑ።
ቢዩኤ ምግቦች - እየጨመረ የመጣው የሽያጭ ገቢ ለራቢው ሀብት ማደግ ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጉ።
ራቢው በቢዩኤ ሲሚንቶ አከፋፋዮች የሽልማት ሥነ-ሥርዓት ላይ ያደረጉትን ንግግር በቪዲዮው ይመልከቱ
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
የ"ቢዩኤ" ግሩፕ መሥራች እና ሊቀመንበር አብዱል ሳማድ ራቢው የሀብት መጠናቸው በግምት 19 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር መድረሱ ተዘግቧል። ይህም ከአሊኮ ዳንጎቴ በመቀጠል በአፍሪካ ሁለተኛው ባለጸጋ ያደርጋቸዋል።
ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ ብቻ ሀብታቸው በ8.88 ቢሊዮን ዶላር የጨመረ ሲሆን፣ ይህም በአኀጉሪቱ ካሉ ቢሊየነሮች መካከል ከፍተኛው የሀብት ዕድገት መሆኑን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ለዚህ አስደናቂ የሀብት ዕድገት ሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ተጠቃሽ ናቸው፦
ቢዩኤ ሲሚንቶ - በአፍሪካ ካሉ ግዙፍ የሲሚንቶ አምራቾች አንዱ መሆኑ።
ቢዩኤ ምግቦች - እየጨመረ የመጣው የሽያጭ ገቢ ለራቢው ሀብት ማደግ ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጉ።
ራቢው በቢዩኤ ሲሚንቶ አከፋፋዮች የሽልማት ሥነ-ሥርዓት ላይ ያደረጉትን ንግግር በቪዲዮው ይመልከቱ
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X