የናይጄሪያው የግዙፍ ኩባንያ ባለቤት በአፍሪካ ሁለተኛው ባለሀብት ሆኑ - መገናኛ ብዙኃን

ሰብስክራይብ
የናይጄሪያው የግዙፍ ኩባንያ ባለቤት በአፍሪካ ሁለተኛው ባለሀብት ሆኑ - መገናኛ ብዙኃን

​የ"ቢዩኤ" ግሩፕ መሥራች እና ሊቀመንበር አብዱል ሳማድ ራቢው የሀብት መጠናቸው በግምት 19 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር መድረሱ ተዘግቧል። ይህም ከአሊኮ ዳንጎቴ በመቀጠል በአፍሪካ ሁለተኛው ባለጸጋ ያደርጋቸዋል።

​ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ ብቻ ሀብታቸው በ8.88 ቢሊዮን ዶላር የጨመረ ሲሆን፣ ይህም በአኀጉሪቱ ካሉ ቢሊየነሮች መካከል ከፍተኛው የሀብት ዕድገት መሆኑን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

​ለዚህ አስደናቂ የሀብት ዕድገት ሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ተጠቃሽ ናቸው፦

ቢዩኤ ሲሚንቶ - በአፍሪካ ካሉ ግዙፍ የሲሚንቶ አምራቾች አንዱ መሆኑ።

ቢዩኤ ምግቦች - እየጨመረ የመጣው የሽያጭ ገቢ ለራቢው ሀብት ማደግ ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጉ።

ራቢው በቢዩኤ ሲሚንቶ አከፋፋዮች የሽልማት ሥነ-ሥርዓት ላይ ያደረጉትን ንግግር በቪዲዮው ይመልከቱ

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0