የሩሲያ አፍሪካ ኮርፕስ እና የማሊ ጦር ስትራቴጂካዊ የድንበር ከተማን ከአሸባሪዎች ነጻ አወጡ

ሰብስክራይብ
የሩሲያ አፍሪካ ኮርፕስ እና የማሊ ጦር ስትራቴጂካዊ የድንበር ከተማን ከአሸባሪዎች ነጻ አወጡ

​ በማሊ እና በኒጀር ድንበር አቅራቢያ የምትገኘው ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያላት ላቤዛንጋ የተባለች የድንበር ከተማ ከአሸባሪዎች ቁጥጥር ነጻ መውጣቷን የሩሲያ ጦር ኃይል አፍሪካ ኮርፕስ አስታውቋል።

​ባለፉት 24 ሠዓታት ውስጥ ጥምር ኃይሉ የሚከተሉትን ተግባራት ሲያከናውን ቆይቷል፡-

​🟠 የጸረ-ሽብር ፍተሻ ኦፕሬሽኖችን ማካሄድ፣

🟠 ሕዝብ በሚበዛባቸው አካባቢዎች ቅኝት እና

🟠 የጭነት ተሽከርካሪዎችን እጀባ።

​ላቤዛንጋን መልሶ ለመቆጣጠር የተደረገው ዘመቻ በሩሲያ የአየር ኃይል የታገዘ ነበር።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0