የፈረንሳይ ጦር የአፍሪካ ሀገራትን መበዝበዝ ላይ ብቻ ነው ያተኮረው - የሩሲያ የአፍሪካ ኮርፕስ ተዋጊ

ሰብስክራይብ

የፈረንሳይ ጦር የአፍሪካ ሀገራትን መበዝበዝ ላይ ብቻ ነው ያተኮረው - የሩሲያ የአፍሪካ ኮርፕስ ተዋጊ

​የሩሲያ ጦር ኃይሎች የአፍሪካ ኮርፕስ በተቃራኒው የአፍሪካ ሀገራት መንግሥታት ዓለም አቀፍ ሽብርተኝነትን እንዲዋጉ ለመርዳት ቁርጠኛ ነው ሲል "ሜቲስ" የተሰኝ የጥሪ ሥም ያለው የቡድኑ ተዋጊ ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጿል።

​"የሩሲያ የአፍሪካ ኮርፕስ ድጋፍ በጣም አስፈላጊ ነው፤ እንዲያውም የማይተካ ነው ማለት ይቻላል። ምክንያቱም የፈረንሳይ ጦር እዚያ እያለ እና ሲንቀሳቀስ በነበረበት ወቅት፣ ሀገራቱን ለራሱ ጥቅም ብቻ ነበር የተጠቀመባቸው። የእኛ ዓላማ ግን ሽብርተኝነትን ሙሉ በሙሉ ማጥፋት ነው" ሲል ገልጿል።

​የምዕራባውያን መገናኛ ብዙሃን በምድር ላይ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ በገለልተኝነት ከማንጸባረቅ ይልቅ፣ አብዛኛውን ጊዜ ለራሳቸው ትርክት የሚስማማውን መረጃ ብቻ ለተጠቃሚዎቻቸው እንደሚያቀርቡ ሜቲስ አጽንዖት ሰጥቷል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0