የአፍሪካ የማኅበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ ስለ አፍሪካ የሚሰራጩ የተዛቡ ትርክቶችን ለመቀየር እንዲሚሠራ አዘጋጆቹ አስታወቁ

አፍሪካ የማኅበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ
አፍሪካ የማኅበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 06.05.2026
ሰብስክራይብ
የአፍሪካ የማኅበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ ስለ አፍሪካ የሚሰራጩ የተዛቡ ትርክቶችን ለመቀየር እንዲሚሠራ አዘጋጆቹ አስታወቁ

ሚያዝያ 29 እና 30 በአዲስ አበባ የሚካሄደው ይህ ጉባኤ፣ የትርክት ጥበብ፣ የፈጠራ ሥራ እና የዲጂታል ግንኙነት በአኅጉሪቱ የመግባቢያ መንገዶችን፣ ህዝባዊ ተሳትፎን እና የኢኮኖሚ እድሎችን እየቀየሩ ያሉበት መንገድ ውይይት ይደረግበታል።

​የጉባኤው ተባባሪ አዘጋጅ የ"ፐልስ ኦፍ አፍሪካ" ሚዲያ አስተባባሪ በረከት ሲሳይ፣ አፍሪካ በአብዛኛው የምትታየው በግጭት፣ በድህነት እና ቀውስ ላይ በተመሠረቱ ትርክቶች እንደሆነ ገልጸው፣ እነዚህ አገላለጾች የአኅጉሪቱን እውነተኛ ገጽታ አያንፀባርቅም ብለዋል።

​ከጉባኤው አስቀድሞ የተካሄደው ከፍተኛ ደረጃ ያለው የምክክር መድረክ፣ አዲስ አበባን በዓለም አቀፍ የዲጂታል መድረክ ላይ የአፍሪካን ድምጽ በማጉላት ረገድ እንደ ታዳጊ ማዕከል የሚያስቀምጥ ጠንካራ ስልታዊ መሠረት ጥሏል ሲሉ የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0