ኢትዮጵያ የቤቶች ልማት ተሞክሮዋን ወደ ጎረቤት ሀገራት ለማስፋፋት ያስችላታል የተባለ ስምምነት ከደቡብ ሱዳን ጋር ተፈራረመች

ኢትዮጵያ፣ ደቡብ ሱዳን
ኢትዮጵያ፣ ደቡብ ሱዳን  - Sputnik አፍሪካ, 1920, 05.05.2026
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የቤቶች ልማት ተሞክሮዋን ወደ ጎረቤት ሀገራት ለማስፋፋት ያስችላታል የተባለ ስምምነት ከደቡብ ሱዳን ጋር ተፈራረመች

የመግባቢያ ሰነዱን የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ረሻድ ከማል እና በደቡብ ሱዳን የማዕከላዊ ኢኳቶሪያ ግዛት መንግሥት አስተዳደሪ ሚስተር ኢማኑኤል አዲል ተፈራርመዋል።

በውሉ መሠረት ኮርፖሬሽኑ በጁባ ከተማ ዘመናዊ የመኖሪያ ቤቶች፣ የንግድ ሕንፃዎችና የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ግንባታ ያከናውናል ተብሏል።

ስምምነቱ የኮርፖሬሽኑን በምሥራቅ አፍሪካና በመላው አኅጉሪቱ ገበያዎች የመሠማራት ራዕይ ወደ ተግባር ያሸጋገረ እንደሆነም ተገልጿል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0