የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉሥ አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ

ጥላሁን ገሠሠ
ጥላሁን ገሠሠ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 05.05.2026
ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉሥ አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ሐውልቱን በአዲስ አበባ ስድስት ኪሎ አካባቢ በይፋ መርቀዋል።

ጥላሁን በኢትዮጲያ ሙዚቃ ታሪክ ትልቅ ቦታ ያለው ሲሆን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ማግኘትም ችሏል። ጥላሁን ገሠሠ ሚያዝያ 11 ቀን 2001 ዓ.ም በ68 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱ ይታወሳል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ መታሰቢያ ሐውልትም ዛሬ ተመርቆ ለሕዝብ ይፋ ሆኗል። የመታሰቢያ ሐውልቱን ከንቲባዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተመሳሳይ መርቀዋል። ድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ሰኔ 22፣ 2012 ዓ.ም አዲስ አበባ ውስጥ በተፈጸመበት ጥቃት በ36 ዓመቱ ህይወቱ ማለፉ ይታወቃል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0