የኬንያ ፕሬዚዳንት በታንጋ ማጣሪያ ዙሪያ ባደረጉት ንግግር በዳሬሰላም ተገሠፁ

የኬንያ ፕሬዚዳንት
የኬንያ ፕሬዚዳንት  - Sputnik አፍሪካ, 1920, 05.05.2026
ሰብስክራይብ
የኬንያ ፕሬዚዳንት በታንጋ ማጣሪያ ዙሪያ ባደረጉት ንግግር በዳሬሰላም ተገሠፁ

ዊሊያም ሩቶ በታንጋ የነዳጅ ማጣሪያ ለመገንባት መታቀዱን ቀድመው ይፋ ማድረጋቸውን ያልወደዱት የታንዛኒያ ፕሬዚዳንት ሳሚያ ሱሉሁ ሀሰን፤ እንዴት ያለኔ መንግሥት እውቅና ይገለጻል ብለው ባልተጠበቀ መንገድ ተቃውሟቸውን አሰምተዋል።


"ውስጥ ስንነጋገር ሩቶን አጥብቄ ጠይቄዋለሁ። በራስህ ስለታንጋ የነዳጅ ማጣሪያ ይፋ አድርገሃል - ለምን ቅድሚያ እኔ አላወቅኩም ነበር? ብዬዋለሁ። ለምን በራሱ ይፋ እንዳደረገው ያስረዳል" ሲሉ በስዋሂሊኛ ተናግረዋል።


ሩቶ የነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካው በአሊኮ ዳንጎቴ የሚደገፍ እና በርካታ ሀገራትን የሚያካትት ክልላዊ ፕሮጀክት እንደሆነ ቀደም ሲል ይፋ አድርገው ነበር።


ሩቶ የተነሳባቸውን ጥያቄ ተከትሎ ውጥረቱን ለማርገብ በሞከሩበት መልሳቸው፤ “በታንጋ የነዳጅ ማጣሪያ ስለመገንባት ይፋ መደረጉ በጣም እንዳስቆጣቸው ተነግሮኛል…ባውቅ ኖሮ የነዳጅ ማጣሪያው በሞምባሳ እንደሚገነባ ይፋ አደርግ ነበር” ብለዋል።


ሁለቱ ሀገራት በመጨረሻም የንግድ ትብብራቸውን ለማሻሻል እና እንቅፋቶችን ለመቀነስ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0