የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት እያጠናከረ ነው - ሚኒስትር

የኢትዮጵያ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ
የኢትዮጵያ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ  - Sputnik አፍሪካ, 1920, 04.05.2026
ሰብስክራይብ
የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት እያጠናከረ ነው - ሚኒስትር

ዘርፉ ሀገሪቱ በውጭ ምርቶች ላይ ያላትን ጥገኝነት ለመቀነስ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል ተናግረዋል።

ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎችና የፖሊሲ ማዕቀፎች የዘርፉን የማምረት አቅም ከፍ እንዳደረጉትና የውጭ ምንዛሪ የሚያድኑ የሀገር ውስጥ ምርቶች መስፋፋታቸውንም ጠቁመዋል።

የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ምክር ቤት መቋቋም አምራቾች የሚያጋጥሟቸውን የፋይናንስና የመሠረተ ልማት ችግሮች በቅንጅት ለመፍታት እገዛ እያደረገ መሆኑንም ሚኒስትሩ አስረድተዋል።

ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት 4ኛው “የኢትዮጵያ ታምርት” ዐውደ ርዕይ ሲከፈት መሆኑን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0