ዚምባብዌ የክረምት ስንዴ አዝመራዋን ለማሳደግ የኤሌክትሪክ ኃይል በ8 በመቶ ጨመረች
17:34 04.05.2026 (የተሻሻለ: 18:38 04.05.2026)

ሰብስክራይብ
ዚምባብዌ የክረምት ስንዴ አዝመራዋን ለማሳደግ የኤሌክትሪክ ኃይል በ8 በመቶ ጨመረች
ዚምባብዌ ከውጭ አስመጪነት ለመውጣትና ከፍተኛ የስንዴ ምርት ለመሰብሰብ በምታደርገው ጥረት፤ ለስንዴ አምራች ገበሬዎች የምታቀርበውን የኃይል አቅርቦት በ8 በመቶ በመጨመር 155 ሜጋ ዋት አድርሳለች። ሀገሪቱ ይህን ግብ ለማሳካት የተሻሻለ መስኖ፣ ሜካናይዜሽን እና የመንግሥት ድጋፍን ተገን አድርጋለች።
የግብርና ሚኒስትሩ ዶክተር አንክሲየስ ማስሁካ፤ የኃይል ድልድሉ የተደረገው ከኢነርጂ ሚኒስቴር ጋር በጋራ ከታቀደ በኋላ እንደሆነና በአሁኑ ወቅት በካሪባ ግድብ የውሃ መጠን በመጨመሩ የሀገሪቱ የኃይል ማመንጨት አቅም በከፍተኛ ሁኔታ መሻሻሉን ገልጸዋል።
ስልታዊ የምግብ ክምችት ለማሳካት ያስችላል ለተባለው ለዚህ ታላቅ ግብ በአሁኑ ወቅት የዘር ሥራ ተጀምሯል። የግብርና እና ገጠር ልማት ባለሥልጣን ከሀገራዊ ግቡ ከግማሽ በላይ የሚሆነውን ድርሻ ይሸፍናል።
ባለሥልጣኑ ለማሳካት ያቀዳቸው ግቦች፦
▪ የኃይል አቅርቦት፦ 155 ሜጋ ዋት (የ8% ጭማሪ)
▪ የምርት ግብ፦ 662,000 ቶን (የ3% ጭማሪ)
▪ ለዘር የታቀደ መሬት፦ 125,000 ሄክታር (የ2.3% ጭማሪ)
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
ዚምባብዌ ከውጭ አስመጪነት ለመውጣትና ከፍተኛ የስንዴ ምርት ለመሰብሰብ በምታደርገው ጥረት፤ ለስንዴ አምራች ገበሬዎች የምታቀርበውን የኃይል አቅርቦት በ8 በመቶ በመጨመር 155 ሜጋ ዋት አድርሳለች። ሀገሪቱ ይህን ግብ ለማሳካት የተሻሻለ መስኖ፣ ሜካናይዜሽን እና የመንግሥት ድጋፍን ተገን አድርጋለች።
የግብርና ሚኒስትሩ ዶክተር አንክሲየስ ማስሁካ፤ የኃይል ድልድሉ የተደረገው ከኢነርጂ ሚኒስቴር ጋር በጋራ ከታቀደ በኋላ እንደሆነና በአሁኑ ወቅት በካሪባ ግድብ የውሃ መጠን በመጨመሩ የሀገሪቱ የኃይል ማመንጨት አቅም በከፍተኛ ሁኔታ መሻሻሉን ገልጸዋል።
ስልታዊ የምግብ ክምችት ለማሳካት ያስችላል ለተባለው ለዚህ ታላቅ ግብ በአሁኑ ወቅት የዘር ሥራ ተጀምሯል። የግብርና እና ገጠር ልማት ባለሥልጣን ከሀገራዊ ግቡ ከግማሽ በላይ የሚሆነውን ድርሻ ይሸፍናል።
ባለሥልጣኑ ለማሳካት ያቀዳቸው ግቦች፦
▪ የኃይል አቅርቦት፦ 155 ሜጋ ዋት (የ8% ጭማሪ)
▪ የምርት ግብ፦ 662,000 ቶን (የ3% ጭማሪ)
▪ ለዘር የታቀደ መሬት፦ 125,000 ሄክታር (የ2.3% ጭማሪ)
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X