በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ዘርፍ ነባራዊ ሁኔታ ላይ ትኩረቱን ያደረገው ዘጋቢ ፊልም ለሁለት ዓለም አቀፍ ሽልማቶች ታጨ

ሰብስክራይብ
በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ዘርፍ ነባራዊ ሁኔታ ላይ ትኩረቱን ያደረገው ዘጋቢ ፊልም ለሁለት ዓለም አቀፍ ሽልማቶች ታጨ

"ሜድ ኢን ኢትዮጵያ" የተሰኘው የፊልም ሥራ ለ47ኛው ኤሚ አዋርድ በንግድና ኢኮኖሚ ዘጋቢ ፊልም ዘርፍ እንዲሁም በዋን ወርልድ ሚዲያ አዋርድ ደግሞ በፊውቸር ዘጋቢ ፊልም ንዑስ ዘርፍ ዕጩ ሆኖ ቀርቧል፡፡

ፊልሙ በአንድ ቻይናዊ የኢንዱስትሪ ፓርክ ዳይሬክተር እንዲሁም በኢትዮጵያውያን ገበሬ እና የፋብሪካ ሠራተኛ መካከል ያለውን ውስብስብ እና አንዳንዴም አስቸጋሪ የሆነ መስተጋብር ይዳስሳል።

አራት ዓመታትን የፈጀው ይህ ፊልም፤ የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ዘርፍ ከግለሰቦች ተሞክሮ እና መነጽር አንጻር የቃኘበት መንገድ ከፍተኛ አድናቆት እንደተቸረው እየተነገረ ይገኛል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0