ሩሲያ በዓለም አቀፍ የአርክቴክቸር እና ዲዛይን ሽልማት የበላይነቱን ያዘች
ሀገሪቱ በዓለም አቀፍ ውድድሮች ገደቦች ቢጣሉባትም፤ በ2026ቱ የዓለም አቀፍ አርክቴክቸር እና ዲዛይን ሽልማት የሩሲያ ፕሮጀክቶች 67 ሜዳሊያዎችን እና የክብር እውቅናዎችን በመሰብሰብ ቀዳሚ ሆነዋል።
ስለ ሽልማቱ ቁልፍ እውነታዎች፦
🟠 በ2026 ከ53 ሀገራት የተውጣጡ ከ500 በላይ ፕሮጀክቶች ቀርበውበታል፣
🟠 ዳኞቹ ከአሜሪካ፣ ቻይና፣ ጣሊያን፣ እንግሊዝ፣ ፈረንሳይ፣ ፖርቱጋል እና ሌሎች ሀገራት የተውጣጡ ባለሙያዎችን ያካተቱ ነበሩ፣
🟠 ሽልማቱ 19 ዘርፎችን የያዘ ሲሆን እያንዳንዱ ዘርፍ ወደ 30 የሚጠጉ ንዑስ ክፍሎች አሉት።
ℹ እ.ኤ.አ በ2019 የተመሠረተው ይህ ሽልማት፤ ከመላው ዓለም የመጡ የፈጠራ ሰዎችን በአንድነት ያገናኛል። ተቋሙ ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑ አሠራሮችን፣ የታዳሽ ኃይል አጠቃቀምን እና ቴክኖሎጂን ከዲዛይን ጋር ማቀናጀትን ያበረታታል።
አንዳንድ ሽልማት ያሸነፉ የሩሲያ ፕሮጀክቶችን ለማየት የስፑትኒክ አፍሪካን ቪዲዮ ይመልከቱ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X