ግብፅ በናይል ደለል አዲስ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ማግኘቷን አስታወቀች

ሰብስክራይብ

ግብፅ በናይል ደለል አዲስ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ማግኘቷን አስታወቀች

እንደ ነዳጅ እና ማዕድን ሀብት ሚኒስቴር መረጃ ከሆነ፤ አዲሱ የጋዝ መስክ በቀን 1.4 ሚሊዮን ሜትር ኩብ ጋዝ እንደሚያመርት ይገመታል።

ቁልፍ ነጥቦች፦

🟠 ከአሁን ቀደም ከነበሩ መሠረተ ልማቶች ጋር ያለው ርቀት በጣም አነስተኛ (ከ2 ኪሎ ሜትር ያነሰ) በመሆኑ ምርቱን በጥቂት ሳምንታት ውስጥ መጀመር ይቻላል፣

🟠 በዘመናዊ የቁፋሮ ቴክኖሎጂ በመታገዙ ወጪን ለመቀነስና ቅልጥፍናን ለመጨመር ተችሏል፣

🟠 ግኝቱ የሀገር ውስጥ የጋዝ አቅርቦትን ለመደገፍ ትልቅ ሚና ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል፣

🟠 ለውጭ አጋሮች የሚከፈለው ሙሉ ክፍያ እስከ ሰኔ ወር መጨረሻ ይጠናቀቃል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ይህም የፍለጋ ሥራዎችን ለማስፋፋት የሚያበረታታ ነው ተብሏል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0