‘ከምዕራባውያኑ ጎራ ጋር የሚያቆራኘንን የትኛውንም ነገር ከእንግዲህ አንፈልግም’ - ኒጀራዊ ባለሙያ
ከወቅታዊው የማሊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ "የአውሮፓ፣ የምዕራባውያን እና የዩክሬን ቅጥረኞች ከአሸባሪዎች ጋር ግንባር ሲገጥሙ የመጀመሪያው አይደለም" ሲሉ የዋፖ ማስተባበሪያ ምክር ቤት አባል አቡባካር አላሳኔ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
"የሌላ ዘመን ቅሪት እና እጅግ የከፋ የጨካኝነት መገለጫ የሆነውን እንዲህ ዓይነቱን ድርጊት አጥብቀን እንኮንናለን" ብለዋል።
እ.ኤ.አ በ2011 የጋዳፊን ህልፈት ተከትሎ ሳኅል በቀውስ እሳት ውስጥ መውደቋን ተናጋሪው አጽንኦት ሰጥተውበታል።
እንደ አላሳን ገለጻ፤ አሁን በሳኅል ቀጣና እየተከሰተ ካለው ሁኔታ ነፃ የሆነ (ስጋት የሌለበት) ሀገር የለም።
ይሁን እንጂ እንዲህ ዓይነት ጥቃቶች ኅብረትን እና አንድነትን በማጠናከር፤ "የአፍሪካ ሕዝብ በተለይም ወጣቱ ከሳኅል ሀገራት ጥምረት ጎን መቆሙን ለዓለም ያሳያል" ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X