‘ፈረንሳይ በሳኅል ቀጣና ስልታዊ ስህተቶችን ፈጽማለች’ - ሴኔጋላዊ የፖለቲካ ተንታኝ

ሰብስክራይብ

‘ፈረንሳይ በሳኅል ቀጣና ስልታዊ ስህተቶችን ፈጽማለች’ - ሴኔጋላዊ የፖለቲካ ተንታኝ

የዓለም አቀፍ ግንኙነት ባለሙያው አማዱ ሞክታር አን፤ "ቋሚ ወታደራዊ ካምፖችን ይዞ መቀጠል፣ የሀገራት መሪዎችን እንደ በታች መመልከት እና የማይጨበጡ የዲሞክራሲ መስፈርቶችን ለመጫን መሞከር" ከፈረንሳይ ስህተቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው ሲሉ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

እንደ ተንታኙ ገለጻ፤ ይህ ሁኔታ የምዕራባውያንን አዲስ የቅኝ አገዛዝ አካሄድ እና በአፍሪካ ሉዓላዊነት ላይ ያለውን ተጽዕኖ በግልጽ ያሳያል።

"ሊካድ የማይችል አንድ እውነት አለ፤ ለ20 ዓመታት በሳኅል ቀጣና የነበረው የምዕራባውያን የደህንነት ተሳትፎ ዘላቂ መረጋጋትን ሊያመጣ አልቻለም" ብለዋል።

በተጨማሪም "የሳኅል ሀገራት ምዕራባውያንን ውድቅ እያደረጉ ነው ባይባልም፤ የሚጠቀሙት የጣልቃ ገብነት ሞዴል ግን "የንቀት" እና "ውጤት አልባ" እንደሆነ ተደርጎ ይታያል ሲሉ ባለሙያው አጽንኦት ሰጥተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0