የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው ከአፍሪካ ቀዳሚ አራት የአቪዬሽን መሪዎች መካከል አንዱ ሆነው ተመረጡ

መስፍን ጣሰው
መስፍን ጣሰው - Sputnik አፍሪካ, 1920, 01.05.2026
ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው ከአፍሪካ ቀዳሚ አራት የአቪዬሽን መሪዎች መካከል አንዱ ሆነው ተመረጡ

ዋና ሥራ አስፈፃሚው ዕውቅናውን ያገኙት በአዲስ አበባ በተካሄደው የዓለም አቀፉ የአየር ትራንስፖርት ማኅበር የ "Focus Africa" ጉባኤ ላይ ነው።

አየር መንገዱን በስኬት በመምራት፣ በ "ቪዥን 2035" ስልታዊ ዕቅድ የአየር መንገዱን አቅም በማሳደግና አዲስ አበባን የአኅጉሪቱ ዋነኛ የአቪዬሽን ማዕከል ለማድረግ ባከናወኑት ተግባር እውቅናው እንደተሰጣቸው ተመላክቷል።

በዝርዝሩ ውስጥ ከአቶ መስፍን በተጨማሪ የናይጄሪያ፣ የኬንያ እና የደቡብ አፍሪካ የአቪዬሽን ዘርፍ ከፍተኛ ኃላፊዎች ተካተዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0