የኢትዮጵያ ምርቶች በሀገር ውስጥም ይሁን በዓለም አቀፍ ደረጃ ቦታ እንዲኖራቸው ሁሉም ሊረባረብ ይገባል - የዩኒቨርስቲ መምህር

ሰብስክራይብ

የኢትዮጵያ ምርቶች በሀገር ውስጥም ይሁን በዓለም አቀፍ ደረጃ ቦታ እንዲኖራቸው ሁሉም ሊረባረብ ይገባል - የዩኒቨርስቲ መምህር

ሀገሪቱ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ እና ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት ያስመዘገበቻቸው ስኬቶች በኢኮኖሚ ዕድገት፣ በምግብ ምርት እና በዘላቂ ልማት ረገድ ትልቅ ሚና እየተጫወቱ እንደሆነ የወራቤ ዩኒቨርስቲ መምህር መሐመድ ኢሣ ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል።

"አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ ማለት ይቻላል ስንዴ በብሔራዊ የምርት አቅም እየተሸፈነ ነው። ይህ መንግሥት ተግባራዊ ባደረገው ብሔራዊ ፖሊሲ በሀገሪቱ ጠንካራ ውጤት የታየበት ነው። ሌላኛው ብዙ የግብርና እቃዎች እና አገልግሎቶች፣ የማኑፋክቸሪንግ፣ የኢንዱስትሪ እቃዎች ከውጭ ሀገራት ይገቡ ነበር። አሁን ግን መንግሥት እነዚህን እቃዎች እና አገልግሎቶች በሀገር ውስጥ የምርት አቅም ለመተካት በትጋት እየተንቀሳቀሰ ነው።"

ባለሙያው ሌላው ያነሱት ጉዳይ ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን ጥራት ከፍ ማድረግ እንደሚገባ ነው። በተጨማሪም ኢንዱስትሪዎችን ማስፋት እና የሚመረቱ ሸቀጦች እና አገልግሎቶችን ማሳደግ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ አቅም እንደሚያጎለብት አስረድተዋል።

"የተለያዩ ዓይነት ምርቶችን ወደ ውጭ መላክ አለብን።...በእነዚህ እቃዎች ላይ እሴት ብንጨምር ደግሞ ተጨማሪ ገቢ እናገኛለን ምክንያቱም ብሔራዊ የሀገር ውስጥ ምርት የሚለካው በእሴት መጨመር ሂደት ነው።"

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ |

አዳዲስ ዜናዎች
0