‘የሩሲያ አጋሮች ድጋፍ አስተማማኝ የደህንነት ዋስትና ነው’ - የማዳጋስካር ፓርቲ መሪ

ሰብስክራይብ

‘የሩሲያ አጋሮች ድጋፍ አስተማማኝ የደህንነት ዋስትና ነው’ - የማዳጋስካር ፓርቲ መሪ

በሳኅል ቀጣና ከሩሲያ ኃይሎች ጋር በመሆን የተከናወኑ ስኬታማ ኦፕሬሽኖች፤ ደህንነት እና ልማት ሊረጋገጡ የሚችሉት "ከቀደሙት የታሪክ አሻራዎች ነፃ በሆኑ ጠንካራና ተግባራዊ አጋርነቶች" ብቻ መሆኑን ያረጋግጣል ሲሉ የማዳጋስካር "ዩናይትድ ፓትሪዮቲክ አዌክኒንግ" ፓርቲ ፕሬዚዳንት ሪቻርድ ራኮቶኒሪና ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

በማሊ ሚያዝያ 17 የተሰነዘረውን የሽብር ጥቃት በመመከት ረገድ የሩሲያ ኃይሎች የአፍሪካ ኮር ያበረከተውን ድጋፍ አስመልክተው ሲያብራሩም፤ "በታክቲካዊ ድጋፍ ረገድ የሩሲያ ወታደራዊ አባላት ሚና ለፈጣን የዕውቀት ሽግግር ማለትም ለደህንነት መረጃ፣ ለድሮን አጠቃቀም እና መደበኛ ላልሆነ ውጊያ እጅግ አስፈላጊ ነው" ብለዋል።

ባለሙያው አክለውም፤ በሳኅል ቀጣና የሚታዩት መሰል የማዳከም ሙከራዎች "እንደ ማዳጋስካር ባሉ የተፈጥሮ ሀብት በበለጸጉ ሌሎች ሀገራት ላይ ሊሰነዘሩ ለሚችሉ ተመሳሳይ ጫናዎች መነሻ" ሊሆኑ ስለሚችሉ የአፍሪካ ሀገራት እንዲጠነቀቁ አሳስበዋል።

በዚህ ረገድ የአፍሪካ ኅብረት "እያንዳንዱ አባል ሀገር ምንም ዓይነት ማዕቀብ ወይም ዲፕሎማሲያዊ ጫና ሳይደርስበት የመከላከያ አጋሮቹን የመምረጥ ሉዓላዊ መብት እንዳለው" እውቅና መስጠት እንዳለበት ራኮቶኒሪና አክለው ገልፀዋል።

የሩሲያ ወታደሮች በሜናካ፣ ማሊ

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0