አንድ ሀገር ለ122 ዓመታት ዕዳ አየከፈለ መኖር የለበትም - ቡርኪና ፋሷዊ የፖለቲካ ተንታኝ

ሰብስክራይብ

አንድ ሀገር ለ122 ዓመታት ዕዳ አየከፈለ መኖር የለበትም - ቡርኪና ፋሷዊ የፖለቲካ ተንታኝ

​የቀድሞዋ የሄይቲ ቅኝ ገዢ ፈረንሳይ የጣለችው የ150 ሚሊዮን የወርቅ ፍራንክ (27 ሚሊዮን ዶላር ገደማ) ዕዳ፤ ሀገሪቱን እንዳሽመደመዳት የቀድሞ የቡርኪና ፋሶ ፓርላማ አባል ኢባ ካሪም ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

​"በወቅቱ ከነበረው የሄይቲ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት ወደ 300 በመቶ የሚጠጋ ዕዳ ለዓመታት መክፈል አይቻልም። በዚህ ሁኔታ በትምህርት፣ በመሠረተ ልማት ወይም በልማት ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ አይቻልም። በዚሁ ዕዳ ምክንያት ሄይቲ በአሜሪካ አኀጉር ድሃዋ ሀገር ሆና ቀጥላለች" ሲሉ አስረድተዋል።

​ዕዳው ባይኖርባት ኖሮ ሄይቲ እንደ ዶሚኒካን ሪፐብሊክ ወይም ኩባ ያለ የእድገት ደረጃ ላይ ልትደርስ ትችል እንደነበር ባለሙያው አክለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0