ማራቶንን ከ2 ሰዓት በታች በመሮጥ የመጀመሪያው ሰው ሆኖ ታሪክ የሠራው ኬናያዊዉ ሰባስቲያን ሳዌ በደማቅ አቀባበል ወደ ሀገሩ ተመለሰ

ሰብስክራይብ

ማራቶንን ከ2 ሰዓት በታች በመሮጥ የመጀመሪያው ሰው ሆኖ ታሪክ የሠራው ኬናያዊዉ ሰባስቲያን ሳዌ በደማቅ አቀባበል ወደ ሀገሩ ተመለሰ

‍ በታሪካዊው የለንደን ማራቶን ውድድር በ1 ሰዓት፣ 59 ደቂቃ እና 30 ሰከንድ አጠናቆ ድል የተቀዳጀው ሳዌን፤ ናይሮቢ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ በሺዎች የሚቆጠሩ አድናቂዎቹ እና የመንግሥት ባለሥልጣናት ደማቅ አቀባበል ያደረጉለት ሲሆን ወላጆቹም የስድስት ሰዓት የመኪና ጉዞ ተጉዘው የልጃቸውን ታሪካዊ ድል በአካል ለመጋራት ተገኝተዋል።

ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ በአጠቃላይ የ8 ሚሊዮን የኬንያ ሽልንግ (62 ሺህ ዶላር) ቼኮች እና ማራቶኑን ያጠናቀቀበት ሰዐት "01:59:30" የሰፈረበት የተሽከርካሪ ታርጋ አበርክተውለታል።

ሳዌ ድሉን ለኬንያ መታሰቢያነት በማድረግ፤ "የሀገራችንን ስም ከፍ ለማድረግ ጥረታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን" ብሏል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0