በማሊ የደህንነት ሁኔታው አሁንም ውጥረት የነገሰበት መሆኑን የሩሲያ ጦር የአፍሪካ ኮር አስታወቀ
16:36 30.04.2026 (የተሻሻለ: 16:54 30.04.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በማሊ የደህንነት ሁኔታው አሁንም ውጥረት የነገሰበት መሆኑን የሩሲያ ጦር የአፍሪካ ኮር አስታወቀ
በጋራ ዕዝ ስር የሚንቀሳቀሱት የ*ጅኒም እና ፍላ* የሽብር ቡድኖች ዳግም በመደራጀት በሩሲያ የአፍሪካ ኮር እና በማሊ ጦር ይዞታዎች ላይ ስለላ እያከናወኑ እንደሚገኙ በማሊ ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ የጦር ክፍሉ ባወጣው መረጃ ገልጿል።
🟠 በሌላ በኩል የ*አይሲሲፒ ታጣቂዎች ሜናካ የተባለችውን ከተማ ለመቆጣጠር ያደረጉት ሙከራ ከከሸፈ በኋላ ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ አላሳዩም።
🟠 ጠላት ከምዕራባውያን ሚዲያዎች ጋር በመቀናጀት በሚያገኘው ገንዘብና ድጋፍ በማሊ ጦር እና በአፍሪካ ኮር ላይ የመረጃ ዘመቻ እየከፈተ ይገኛል።
🟠 የማሊ ጦር ክፍሎች በሰባቡጉ ሰፈራ በ "ጂኒም" ታጣቂዎች የተሰነዘረውን ጥቃት በስኬት መክተዋል።
🟠 የሩሲያ የአፍሪካ ኮር ከማሊ ወታደራዊ ኃይሎች ጋር በመሆን የስለላ እና የተለዩ የጠላት ኢላማዎችን የማጥፋት እርምጃቸውን ቀጥለዋል።
*በሩሲያ እና በሌሎች በርካታ ሀገራት በሕገ-ወጥነት የተፈረጁ የሽብር ድርጅቶች
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia