ኢትዮጵያዊው የድህረ-ምረቃ ተማሪ በሁለተኛው ዓለም አቀፍ ነፃ የውይይት መድረክ ላይ ባቀረበዉ ጥናታዊ ፅሁፍ አሸናፊ ሆነ

ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያዊው የድህረ-ምረቃ ተማሪ በሁለተኛው ዓለም አቀፍ ነፃ የውይይት መድረክ ላይ ባቀረበዉ ጥናታዊ ፅሁፍ አሸናፊ ሆነ

በአዲስ የዓለም የዕድገት ሞዴል ላይ የሚወያየው ይህ መድረክ፤ ከ120 ሀገራት በላይ የተውጣጡ ከ3 ሺህ በላይ ባለሙያዎችን አሳትፎ ከሚያዚያ 19 እስከ 21 በሞስኮ "መጻኢው የዓለም ሁኔታ፤ ለዓለም አቀፍ ዕድገት አዲስ መድረክ" በሚል መሪ ቃል ተካሂዷል፡፡

ነፃ የውይይት መድረኩ በአራት ቁልፍ መስኮች የተዋቀረ ነበር፦

በሰዎች ላይ ኢንቨስት ማድረግ፣

በቴክኖሎጂ ላይ ኢንቨስት ማድረግ፣

በአካባቢ ላይ ኢንቨስት ማድርግ፣

ግንኙነት ላይ ኢንቨስት ማድረግ፡፡

ኢትዮጵያዊው ሰለሞን ጋርዴ “ግንኙነት ላይ ኢንቨስት ማድረግ” በሚለው ዘርፍ ያቀረበው ጽሁፍ አሸናፊ ሆኗል።

ፕሬዚዳንት ፑቲን ለፎረሙ ተሳታፊዎች ባስተላለፉት መልዕክት፤ “የዓለም አቀፍ ልማት ሞዴል ዘላቂ የሚሆነው በእኩልነት መርሆዎች ላይ የተመሠረተ እና የሁሉንም ሀገራት ጥቅም ግምት ውስጥ ሲያስገባ ነው” ሲሉ ተናግረው ነበር፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0