በማሊ የተፈጸሙ ጥቃቶች፦ አፍሪካ "ለእውነተኛ ሉዓላዊነት መታገል አለባት" ሲሉ የካሜሩን ፖለቲከኛ ገለጹ

ሰብስክራይብ

በማሊ የተፈጸሙ ጥቃቶች፦ አፍሪካ "ለእውነተኛ ሉዓላዊነት መታገል አለባት" ሲሉ የካሜሩን ፖለቲከኛ ገለጹ

​በካሜሩን የፒዩአርኤስ ፓርቲ ተቀዳሚ ፀሐፊ ሰርጅ ኤስፕዋር ማቶምባ በሞስኮ በተካሄደው የመጀመሪያው "የሶቪንተርን" ፎረም ጎን ለጎን ለስፑትኒክ አፍሪካ እንደተናገሩት፤ “አፍሪካውያን የሳህል ሀገራት ጥምረት አባል ሀገራትን ኢላማ ያደረጉ ማንኛውንም የፀረ-መረጋጋት ተግባራት ለማክሸፍ መተባበር አለባቸው” ብለዋል።

ፖለቲከኛው አክለውም፣ “ለካፒታሊስት ፍላጎቶች እና ለምዕራባውያን ሀገራት ጥቅም ካልሆነ በስተቀር ለምን ሁልጊዜ እነዚህን ሀገራት ማናጋት ይፈልጋሉ?” ሲሉ ጥያቄ አንስተዋል።

​ካፒታሊዝም ዓለምን ስላጠፋ ዛሬ አዲስ ስምምነትና አዲስ ንቅናቄ ያስፈልጋል ሲሉም ገልጸዋል።

​“ይህ የሶቪንተርን ፎረም ተነሳሽነት የመጣው በሶሻሊዝም የሚታወቁት ሃሳቦች እና እሴቶች በዓለም ዜጎች ልማድ ውስጥ ስር መስደድ በሚገባቸው ወቅት ላይ ነው” ሲሉ አስረድተዋል ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0