የኤስዋቲኒው ንጉሥ መስዋቲ ሣልሳዊ 58ኛ ዓመት የልደት እና 40ኛ ዓመት የንግሥና በዓላቸውን አከበሩ
19:00 27.04.2026 (የተሻሻለ: 19:04 27.04.2026)
ሰብስክራይብ
የኤስዋቲኒው ንጉሥ መስዋቲ ሣልሳዊ 58ኛ ዓመት የልደት እና 40ኛ ዓመት የንግሥና በዓላቸውን አከበሩ
እ.ኤ.አ. በ1986 በ18 ዓመታቸው የነገሡት ንጉሥ መስዋቲ ሣልሳዊ በኤስዋቲኒ ታሪክ ረጅሙን ጊዜ የገዙ ንጉሥ ሲሆኑ፣ በአሁኑ ወቅትም በዓለም ላይ ካሉ ጥቂት ፍጹም (ጠቅላይ) ንጉሣውያን መካከል አንዱ ናቸው።
ከሚያዝያ 17 እስከ 19 የሚካሄደው ይህ ድርብ ክብረ በዓል፣ ባህላዊ ሥነ-ሥርዓቶችን፣ የባህል ትርኢቶችን እና አገራዊ ድግሶችን በመላው ግዛቱ አሰባስቧል።
በበዓሉ ላይ ከተገኙት የውጭ አገር መሪዎች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፦
የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ፣
የሞዛምቢኩ ፕሬዝዳንት ዳንኤል ቻፖ፣
የቦትስዋናው ፕሬዝዳንት ዱማ ቦኮ እና
የዚምባብዌው ፕሬዝዳንት ኤመርሰን ምናንጋግዋ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X