ደቡብ አፍሪካ የነፃነት ቀንን እያከበረች ነው

ደቡብ አፍሪካ የነፃነት ቀንን እያከበረች ነው
ደቡብ አፍሪካ የነፃነት ቀንን እያከበረች ነው - Sputnik አፍሪካ, 1920, 27.04.2026
ሰብስክራይብ
ደቡብ አፍሪካ የነፃነት ቀንን እያከበረች ነው

​ በጎርጎሮሳዊያኑ ሚያዝያ 27 ቀን 1994 ሁሉም ደቡብ አፍሪካውያን ዘር ሳይለይ ለመጀመሪያ ጊዜ በነፃነት በመረጡበት ምርጫ ሕገ-መንግሥታዊ ዲሞክራሲያቸውን አበሰሩ።

የምርጫው ውጤት የሚከተለውን ይመስል ነበር፦

▪​ወደ 20 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ድምጽ ሰጥተዋል፡፡
▪​ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ምርጫው ነፃ እና ፍትሃዊ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡
▪​የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ አሸናፊ ሆኗል፡፡
▪​ኔልሰን ማንዴላ የደቡብ አፍሪካ የመጀመሪያው በዲሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጡ ፕሬዝዳንት ሆነው ተሾሙ።

​ ይህ ቀን ደቡብ አፍሪካ ለረጅም ጊዜ ከቆየው የቅኝ ግዛት፣ የአፓርታይድ እና በእነዚህ ስርዓቶች አማካኝነት ከነበረው የነጮች አናሳ ቡድን የበላይነት ነፃ የወጣችበትን ዕለት ያመለክታል።


​ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ በብሉምፎንቴን በተካሄደው ብሔራዊ በዓል ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ​"ዛሬ እዚህ የቆምነው የዲሞክራሲያዊት ሀገር ዜጎች በመሆናችን ብቻ ሳይሆን፣ በከባድ ትግል የተገኘው የነፃነት ቅርስ ጠባቂዎችም በመሆናችን ነው። ይህ ቅርስ በትግል የተገኘ፣ በመስዋዕትነት፣ በፅናት እና በነፃነት እንዲሁም በፍትሕ ላይ በነበረ የማይናወጥ እምነት የተቀረፀ ነው።" ብለዋል፡፡


በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0